የኮሚሽነር ጄኔራል መልዕክት

Commissioner Image

የተከበራችሁ ውድ የሀገራችን ህዝቦች፣ የተከበራችሁ መላው የሃገራችን ፖሊስ አመራር እና አባላት እንዲሁም አጋር የፀጥታ አካላት በአሁኑ ወቅት ሀገራችን ኢትዮጵያ በፖለቲካ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የለውጥ ሂደት ላይ ትገኛለች።

ዝርዝር መልዕክት

አዳዲስ ዜናዎች!

  • የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የህጻናት ማቆያ አስመርቆ ሥራ አስጀመረ( Federal News)

    አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 06 ቀን 2015 ዓ.ም (ኢፌፖሚ)፡-የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የህፃናት ማቆያ (ዴይ ኬር) በወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ ቅጥር ግቢ አስመርቆ ሥራ አስጀመረ፡፡

    በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት ክቡር የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የወቅቱ የምስራቅ አፍሪካ ፖሊስ አዛዦች ኅብረት ድርጅት ፕሬዚዳንት በህፃናት ማቆያ ህፃናቶቻችንን ስናቆይ ከሁሉም የፖሊስ ቤተሰብ ጋር እየተገናኙ አብሮ የሚያድጉ በመሆኑ የተሻለ ጠንካራ የፖሊስ ቤተሰብ ከመፍጠሩም ባሻገር ነገ ለምናስባት ኢትዮጵያ መሠረት የሚጥል ስለሆነ ሥራው በስፋት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።

    የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ ከሌሎች ሥራዎች ጎን ለጎን የህፃናት ማቆያዉ እንዲሰራ ማድረጉ መልካም አርዓያ መሆኑን ተናግረው አሁን እያስቸገረን ያለዉን በብሔር፣ በሀይማኖት እና በፖለቲካ የሚፈጠሩ ልዩነቶችን ማጥበብ የሚቻለው እና ነገ የተሻለች ኢትዮጵያን ለማየት ዛሬ በልጆቻችን ላይ ስንሰራ መሆኑን ተናግረዋል ።

    ሁሉም ጠቅላይ መምሪያዎች በቀጣይ ከዚህ ተሞክሮ ወስደው የራሳቸው የህፃናት ማቆያ ማዕከላት እንዲኖራቸው በማድረግ የሴት ፖሊስ አመራር እና አባላት ልጆቻቸውን በቅርበት እየተከታተሉ ሥራቸውን በነፃነት መስራት እንዲችሉ ማድረግ ይኖርባቸዋል ብለዋል።

  • የፀጥታ አካላት ሕዝባዊ ሚሊሻን መልሶ ለማደራጀት እና ቀደም ሲል የተጀመረው የልዩ ኃይል መልሶ የማደራጀት ሥራ በምን ደረጃ ላይ እንዳለ ለመገምገም ውይይት አካሄዱ( Federal News)

    አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18 ቀን 2015 ዓ.ም (ኢፌፖሚ)፡ የፀጥታ አካላት ሕዝባዊ ሚሊሻን መልሶ ለማደራጀት እና ቀደም ሲል የተጀመረው የልዩ ኃይል መልሶ የማደራጀት ሥራ በምን ደረጃ ላይ እንዳለ ለመገምገም በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዋና መሥሪያ ቤት ውይይት አካሄዱ።
    ሕዝባዊ ሚሊሻን መልሶ ለማደራጀት እና ቀደም ሲል የተጀመረው የልዩ ኃይል መልሶ ማደራጀት ሥራ በምን ደረጃ ላይ እንዳለ ለመገምገም በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ የሀገር መከላከያ ከፍተኛ መኮንኖች፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮች፣ የክልል ፖሊስ ኮሚሽነሮች፣ የአዲስ አበባና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽነሮች እና የክልል የፀጥታ ቢሮ ኃላፊዎች በውይይቱ ላይ ተሳትፈዋል።

  • በሕገ-ወጥ መንገድ ከ5 ቢሊየን ብር በላይ ሲያንቀሳቅስ የነበረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለፀ( Federal News)

    አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 16 ቀን 2015 ዓ.ም (ኢፌፖሚ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኅብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማና ባደረገው ብርቱ ክትትል በህገ-ወጥ መንገድ መንገድ ከ5 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር (ከአምስት ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር) በላይ ሲያንቀሳቅስ የነበረ ግለሰብ ከ25 ግብረ-አበሮቹ ጋር የገንዘብ ልውውጥ ያደርግ መሆኑ አረጋግጦ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራበት መሆኑን ገለፀ፡፡

    በወንጀሉ የተጠረጠረው ሳሙኤል እጓለ አለሙ በቅፅል ስሙ ሳሚ ዶላር የሚባል ሲሆን ነዋሪነቱን በአዲስ አበባ ከተማ በማድረግ ወደ አሜሪካን ሀገር በተደጋጋሚ የሚመላለስ የኤሌክትሪክ መሳሪያዎች፣ የቤት እና የቢሮ እቃዎች እንዲሁም ተዛማጅ መገልገያዎች የችርቻሮ ንግድ ፍቃድን ሽፋን በማድረግ ሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሬና በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር ወንጀል ተጠርጥሮ በራሱና ዮዲት እጓለ አለሙ ከተባለች እህቱ ጋር በመሆን በስማቸው በተለያዩ ባንኮች በከፈቷቸው ሃያ አምስት የባንክ አካውንቶች በአንድ ዓመት ውስጥ ከ247 ሚሊየን ብር (ሁለት መቶ አርባ ሰባት ሚሊየን ብር) በላይ ማንቀሳቀሳቸውን ፖሊስ ደርሶባቸው ምርመራ እየተጣራባቸው መሆኑ ታውቋል፡፡

  • ኢትዮጵያ በ90ኛው ዓለም አቀፍ የፖሊስ ድርጅት (INTERPOL) ጠቅላላ ጉባኤ ተሳተፈች( Federal News)

    ህንድ፣ ኒውደልሂ፣ ጥቅምት 11 ቀን 2015 ዓ.ም (ኢፌፖሚ) - በህንድ ኒውደልሂ ከተማ እ.ኤ.አ ከጥቅምት 18 እስከ 21 ቀን 2022 በተካሄደው 90ኛው ዓለም አቀፍ የፖሊስ ድርጅት (INTERPOL) ጠቅላላ ጉባኤ ኢትዮጵያ ተሳትፋለች።

    በጉባዔው የ188 አባል ሀገራት ፖሊስ አዛዦች፣ ፖሊስ ተጠሪ የሆኑላቸው ሚኒስትሮች እና የተለያዩ ከፖሊስ ጋር በአጋርነት የሚሰሩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የተሳተፉ ሲሆን ክቡር የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የተመራ ልዑካን ቡድንም ተሳትፏል።

  • የክቡር ኮሚሽነር ጀነራል መልዕክት( Commissioner Message)

    የተከበራችሁ ውድ የሀገራችን ህዝቦች፣ የተከበራችሁ መላው የሃገራችን ፖሊስ አመራር እና አባላት እንዲሁም አጋር የፀጥታ አካላት በአሁኑ ወቅት ሀገራችን ኢትዮጵያ በፖለቲካ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የለውጥ ሂደት ላይ ትገኛለች።

  • የአዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት( Commissioner Message)

    የአዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት

    በቅድሚያ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብና ለሀገራችን የፖሊስ አባላት እንኳን ለ2015 ዓ.ም በሰላምና በጤና አደረሳችሁ እያልኩ፤ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ መላውን ሕዝብ ከጎኑ አሰልፎ በአዲስ ዓመት ካለፈው የተሻለ አንፀባራቂ ውጤት በማስመዝገብ የኢትዮጵያን ብሩህ ተስፋና የተቋማችንን ከፍታ የሚያረጋግጥበት ዘመን እንደሚሆን ሙሉ እምነት አለኝ።

የሚሰጡ አገልግሎቶች

ወንጀል መከላከል


የፌዴራል መንግሥት ተቋማትን ይጠብቃል፤ ለከፍተኛ የፌዴራሉ መንግሥት ባለሥልጣናት፣ ለውጭ አገር የክብር እንግዶችና ዲፕሎማቶች ጥበቃ ያደርጋል፤


አስተዳደርና ልማት


በፖሊስ ምልመላና ቅጥር፣ በትምህርትና ሥልጠና፣ በማዕረግ አሰጣጥ፣ በደንብ ልብስ አለባበስ፣ በትጥቅና ሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮች ሀገር አቀፍ ደረጃዎችን ያወጣል፤


ወንጀል ምርመራ


የወንጀል ምርመራን በተመለከተ ከፍትሕ ሚኒስቴርና ከሚመለከታቸው ሌሎች አካላት ጋር በጋራ ይሠራል፤


ወንጀል መከላከል


በሕገ-መንግሥቱና ሌሎች ህጎችን፣ በመንግሥትና በሀገር ፀጥታ እና በሰብዓዊ መብት ላይ የሚፈፀሙ ማናቸውም ዓይነት የወንጀል ስጋቶችና ድርጊቶችን ይከላከላል፡፡