የኮሚሽነር ጄኔራል መልዕክት

Commissioner Image

በቅድሚያ እንኳን ለ116ኛው ሀገር አቀፍ የኢትዮጵያ ፖሊስ ቀን አደረሳችሁ አደረሰን!

ዝርዝር መልዕክት

አዳዲስ ዜናዎች!

  • የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር በፀጥታና ደህንነት፣ በቴክኖሎጂ፣ በትምህርትና ስልጠና እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረመ( Federal News)

    ‎አዲስ አበባ፣ የካቲት 26 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር በፀጥታና ደህንነት፣ በቴክኖሎጂ፣ በትምህርትና ስልጠና እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ በዛሬው ዕለት በዋና መሥሪያ ቤት ተፈራርሟል።

  • ከህንዳዊ ዜጋ የሞባይል ስልክ የሰረቁ ተጠርጣሪዎች በስማርት ፖሊስ ስቴሽን (SPS) አማካኝነት በቁጥጥር ስር ዋሉ( Federal News)

    አዲስ አበባ፣ የካቲት 25 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ) ‎በአዲስ አበባ ከተማ ኦሎምፒያ አደባባይ የሞባይል ስልክ የተሰረቀው ህንዳዊ ጉዳዩን በስማርት ፖሊስ ስቴሽን (SPS) አማካኝነት ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ያመለክታል። ፖሊስም የተበዳዩን አቤቱታ መሠረት በማድረግ ባካሄደው ክትትል ወንጀሉን የፈፀሙ ግለሰቦችን በቁጥጥር ሥር በማዋል ንብረቱን ለባለቤቱ ማስረከብ ችሏል።

  • “ጠንካራ የምርምር ባህልን ለመገንባት በትኩረት እየተሰራ ነው” ክቡር ታምራት ሙሉጌታ (ዶክተር)( Federal News)

    ስንዳፋ፣ የካቲት 24 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ) የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ክቡር ታምራት ሙሉጌታ (ዶክተር) ​ጠንካራ የምርምር ባህልን ለመገንባት በትኩረት እየተሰራ ነው ያሉት በዩኒቨርሲቲው ሙያዊ ብቃትንና የአካዳሚክ ልህቀትን ለማሳደግ እንዲሁም በማስረጃ ላይ የተመሰረተ የፖሊስ አገልግሎትን ለመስጠት በተካሄደ የምርምር ሴሚናር ላይ ተገኝተው ፕሮግራሙን ባስጀመሩበት ወቅት ነው።

  • “ኢትዮጵያዊነት በዓድዋ ሚዛን ሲመዘን ሕይወትን በመለገስ የፀና፣ በላብ የጠነከረ፣ በዕውቀታችን እና በአርቆ አሳቢነታችን የሚለመልም ህያው ማንነት ማለት ነው” የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዝዳንት ታየ አጽቀሥላሴ( Federal News)

    አዲስ አበባ፣ የካቲት 23 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ) ኢትዮጵያዊነት በዓድዋ ሚዛን ሲመዘን ሕይወትን በመለገስ የፀና፣ በላብ የጠነከረ፣ በዕውቀታችን እና በአርቆ አሳቢነታችን የሚለመልም ህያው ማንነት ማለት ነው ሲሉ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዝዳንት ታየ አጽቀሥላሴ ገልፀዋል፡፡

  • የአፍሪካ ሀገራት መከላከያ ሚኒስትሮች፣ አምባሳደሮች፣ ወታደራዊ አታሼዎች፣ የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግሥታት ተጋባዥ እንግዶች የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ሰው አልባ ስማርት ፖሊስ ስቴሽንን ጎበኙ( Federal News)

    አዲስ አበባ፣ የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ) የአፍሪካ ሀገራት መከላከያ ሚኒስትሮች፣ አምባሳደሮች፣ ወታደራዊ አታሼዎች፣ የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግሥታት ተጋባዥ እንግዶች የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ሰው አልባ ስማርት ፖሊስ ስቴሽንን በዛሬው ዕለት ጎብኝተዋል፡፡

  • "ግዙፍ የምርመራ ኢንስቲትዩቶችን በመገንባት ለነገ ትውልድ የሚሻገር ታሪካዊ የተቋም ግንባታ ሥራ እየተሰራ ነው" ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል( Federal News)

    አዲስ አበባ፣ የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ከለውጡ በፊት ኋላ ቀር የነበረውን የታክቲክና የቴክኒክ የምርመራ ሥራ ዛሬ ላይ ከሀገራችን አልፎ ለሌሎች ሀገራት የሚተርፍ፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ጥቂት ሀገሮች ብቻ ያላቸውን ዘመናዊ ቴክኖሎጅዎችን የሚጠቀም እንዲሁም ግዙፍ የምርመራ ኢንስቲትዩቶችን በመገንባት ለነገ ትውልድ የሚሻገር ታሪካዊ የሆነ የተቋም ግንባታ ሥራ እየተሠራ መሆኑን የገለፁት በወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ አመራርና ባለሙያዎች የሥራ ግምገማ ላይ ነው።

የሚሰጡ አገልግሎቶች

የሚሰጡ አስተዳደራዊ አገልግሎቶች


  1. ጥቆማና አቤቱታ መቀበልና የአቅራቢዎችን ቃል መቀበል
  2. የህዝብ ክንፍ መድረክ በማዘጋጀት የዜጎችን መረጃ የማግኘት መብት ማረጋገጥና የተቋሙን አፈጻጸም እንዲገመግሙ ማድረግ


በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጡ አገልግሎቶች


  1. የማህበረሰብ አገልግሎት (Community Service) ስራዎችን ማከናወን፣
  2. ስለወንጀል መከላከልና ምርመራ ሀገር አቀፍ ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችንና አንድ ወጥ የሆኑ የአሠራር ደረጃዎችን ማዘጋጀት


በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጤና አገልግሎት የሚሰጡ አገልግሎቶች


  1. የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት ለሰራዊቱና ለህግ ታራሚዎች መስጠት፤
  2. የተኝቶ ህክምና አገልግሎት መስጠት


በወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የሚሰጡ አገልግሎቶች


በክስ መቀበል አገልግሎት

  1. የወንጀል ጥቆማዎችንና አቤቱታዎችን መቀበል፣
  2. የቀረበው አቤቱታ ጥቆማ ወንጀል መሆን አለመሆኑን እና በፌደራል የማጣራት ስልጣን ስር የሚወድቅ መሆን አለመሆኑን መወሰን፣