የኮሚሽነር ጄኔራል መልዕክት

Commissioner Image

በቅድሚያ እንኳን ለ116ኛው ሀገር አቀፍ የኢትዮጵያ ፖሊስ ቀን አደረሳችሁ አደረሰን!

ዝርዝር መልዕክት

አዳዲስ ዜናዎች!

  • የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰላም እንዲጠናቀቅ የጋራ የፀጥታ ዕቅድ ላይ ውይይት ተካሄደ( Federal News)

    አዲስ አበባ፣ ሰኔ 09 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ)፡-የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰላም እንዲጠናቀቅ የጋራ የፀጥታ ዕቅድ ላይ ውይይት ተካሄዷል፡፡

  • የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ለጣናነሽ-2 ጀልባ እያደረገ ያለውን እጀባ አጠናክሮ ቀጥሏል( Federal News)

    አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8 ቀን 2017 ዓ.ም:- የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ለጣናነሽ-2 ጀልባ እያደረገ ያለውን እጀባ አጠናክሮ ቀጥሏል።

    የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የአፋር ክልል እና የኦሮሚያ ክልል ከተሞችን እያቆራረጠች ጉዞዋን ስታደርግ ለቆየችው ጣናነሽ-2 ጀልባ የተሳካ ጉዞ እንድታደርግ ሌት ተቀን የተጠናከረ እጀባ እያደረገላት ይገኛል።

  • የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጤና አገልግሎት ዋና መምሪያ ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ድጋፍ አደረገ( Federal News)

    አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5 ቀን 2017 ዓ.ም(ኢፌፖሚ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጤና አገልግሎት ዋና መምሪያ ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ድጋፍ ያደረገው በሀገራችን ለ43ኛ በዋና መምሪያው ደግሞ ለ4ኛ ጊዜ የተከበረውን የዓለም የነርሶችና የአዋላጅ ነርሶች ቀንን ምክንያት በማድረግ ነው።

  • የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጤና አገልግሎት ዋና መምሪያ በዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ (Mpox) ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ( Federal News)

    አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጤና አገልግሎት ዋና መምሪያ ጤና ማበልጸግ፣ በሽታ መከላከልና ክሊኒኮች መምሪያ በዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ (Mpox) ላይ ከመምሪያ በላይ ላሉ ከፍተኛ አመራሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በዋና መሥሪያ ቤት ሰጥቷል።

  • ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የተሰጠ ወቅታዊ መረጃ( Federal News)

    በትላንትናው ዕለት በአዲስ አበባ ስታዲየም በሲዳማ ቡናና ወላይታ ዲቻ መካከል የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍጻሜ የእግር ኳስ ውድድር መካሄዱ ይታወሳል፡፡

    ሁለቱን ክለቦች ለመደገፍ ከሀዋሳ፣ ከወላይታ ሶዶ እና ከአካባቢው የመጡ በርካታ ደጋፊዎች መካከል አለመግባባት በመፈጠሩ ጨዋታው በዝግ ስታዲየም እንዲካሄድ ተደርጎ ፖሊስ በደጋፊዎች መካከል ይፈጠር የነበረውን ግጭት በማስቀረት አስፈላጊውን ወቅታዊና ሕጋዊ ተግባር በመፈፀም ሕግና ሥርዓት አስከብሯል፡፡

    ነገር ግን የሀገራችን ሰላምና መረጋጋት የሚመራቸው በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ያሉ አካላት ተናበው የሰዎች ሕይወት እንዳለፈ አስመስለው በመዘገብ ግጭት ለማባባስ እየሞከሩ እንደሆነ ታዝበናል፡፡

  • "የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የጦር መሣሪያ ጥገና ኦርዲናንስ ክፍል ለሀገራችን ፖሊስ ተቋማት እንደ ሞዴልና የለውጥ ተምሳሌት ሆኖ የሚታይ ነው።" ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ ሚካኤል( Federal News)

    አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ)፡- ክቡር የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የጦር መሳሪያ ጥገና ኦርዲናንስ ክፍል ለሀገራችን ፖሊስ ተቋማት እንደ ሞዴልና የለውጥ ተምሳሌት ሆኖ የሚታይ ነው ያሉት በትላንትናው ዕለት የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በሪፎርሙ ያከናወናቸውን የለውጥ ስራዎች ተዘዋውረው በጎበኙበት ወቅት ነው።

የሚሰጡ አገልግሎቶች

የሚሰጡ አስተዳደራዊ አገልግሎቶች


  1. ጥቆማና አቤቱታ መቀበልና የአቅራቢዎችን ቃል መቀበል
  2. የህዝብ ክንፍ መድረክ በማዘጋጀት የዜጎችን መረጃ የማግኘት መብት ማረጋገጥና የተቋሙን አፈጻጸም እንዲገመግሙ ማድረግ


በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጡ አገልግሎቶች


  1. የማህበረሰብ አገልግሎት (Community Service) ስራዎችን ማከናወን፣
  2. ስለወንጀል መከላከልና ምርመራ ሀገር አቀፍ ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችንና አንድ ወጥ የሆኑ የአሠራር ደረጃዎችን ማዘጋጀት


በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጤና አገልግሎት የሚሰጡ አገልግሎቶች


  1. የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት ለሰራዊቱና ለህግ ታራሚዎች መስጠት፤
  2. የተኝቶ ህክምና አገልግሎት መስጠት


በወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የሚሰጡ አገልግሎቶች


በክስ መቀበል አገልግሎት

  1. የወንጀል ጥቆማዎችንና አቤቱታዎችን መቀበል፣
  2. የቀረበው አቤቱታ ጥቆማ ወንጀል መሆን አለመሆኑን እና በፌደራል የማጣራት ስልጣን ስር የሚወድቅ መሆን አለመሆኑን መወሰን፣