የኮሚሽነር ጄኔራል መልዕክት

የተከበራችሁ ውድ የሀገራችን ህዝቦች፣ የተከበራችሁ መላው የሃገራችን ፖሊስ አመራር እና አባላት እንዲሁም አጋር የፀጥታ አካላት በአሁኑ ወቅት ሀገራችን ኢትዮጵያ በፖለቲካ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የለውጥ ሂደት ላይ ትገኛለች።
ዝርዝር መልዕክትአዳዲስ ዜናዎች!
-
በሀገራችን በቅርቡ የሚካሄደውን 38ኛውን የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤንና የትላልቅ ሁነቶችን ደህንነት ለመምራት የሚያስችል ሴሚናር (SEMINAR ON LARGE EVENT SECURITY MANAGEMENT) እየተካሄደ ነው( Federal News)
አዲስ አበባ፣ ጥር 26 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ) በሀገራችን በቅርቡ የሚካሄደውን 38ኛውን የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤን ጨምሮ ትላልቅ ሁነቶችን ደህንነት ለመምራት የሚያስችል በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እና በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ በጋራ በተዘጋጀ ሴሚናር ላይ የልምድ ልውውጥ እና ስልጠና በዋና መሥሪያ ቤት እየተካሄደ ይገኛል።
-
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሲካሄድ የቆየው የስትራቴጂክ እና የከፍተኛ አመራር የፖሊስ መኮንኖች ስብሰባ በዛሬው ዕለት ተጠናቋል( Federal News)
ሰንዳፋ፣ ጥር 24 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ) ክቡር የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በስብሰባው ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው በሰጡት የሥራ መመሪያ በዚህ በሪፎርም ጊዜ ሕዝቡ የሚፈልገው ፖሊስ፤ በጣም ዲሲፕሊን የሆነ፣ የማይሰርቅ፣ አለባበሱ የሚያምር፣ ሥርዓት ያለው፣ ዘመኑን የዋጁ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም የሚችል እና የትም ቦታ ሄዶ ወንጀል መከላከል የሚችል ብቃት ያለው፣ በዘር የማያምን፣ ከፖለቲካና ከሀይማኖት ወገንተኝነት የፀዳ ፖሊስ ነው ብለዋል።
-
ተባበሩት ዐረብ ኢምሬቶች ባዘጋጀቺው የዓለም አቀፍ የ2025 SWAT Challenge ላይ ለመወዳደር ወደ ዱባይ ያቀናው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ SWAT ቡድን ልምምድ እያደረገ ነው( Federal News)
አልሩዋይ ከተማ ዱባይ፣ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ) የተባበሩት ዐረብ ኢምሬቶች ባዘጋጀቺው የዓለም አቀፍ የ2025 SWAT Challenge ላይ ለመወዳደር ወደ ዱባይ ያቀናው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ SWAT ቡድን በዱባይ አልሩዋይ ከተማ በሚገኘው የSWAT Challenge ማሰልጠኛ ማዕከል ልምምድ እያደረገ ይገኛል።
-
"የኢትዮጵያ ፖሊስ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሰላምና ደህንነት እንዲረጋገጥና መንግስት ያቀዳቸው የልማት ስራዎች እንዲከወኑ ትልቅ ድርሻ አበርክቷል።" ክቡር ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፋንታ( Federal News)
አዲስ አበባ፣ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ) የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ክብር ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፋንታ የኢትዮጵያ ፖሊስ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሰላምና ደህንነት እንዲረጋገጥና መንግስት ያቀዳቸው የልማት ስራዎች እንዲከወኑ ትልቅ ድርሻ አበርክቷል ያሉት የተቋሙ ስትራቴጂክ አመራሮች እና የፖሊስ መኮንኖች ባለፉት ስድስት ዓመታት በተቋሙ ሲተገበር የቆየው የለውጥ ሂደት ላይ ለመወያየት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በተዘጋጀው የውይይት መርሃ ግብር ላይ ነው፡፡
-
"የኢትዮጵያ ፖሊስ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሰላምና ደህንነት እንዲረጋገጥና መንግስት ያቀዳቸው የልማት ስራዎች እንዲከወኑ ትልቅ ድርሻ አበርክቷል።" ክቡር ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፋንታ( Federal News)
አዲስ አበባ፣ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ) የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ክብር ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፋንታ የኢትዮጵያ ፖሊስ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሰላምና ደህንነት እንዲረጋገጥና መንግስት ያቀዳቸው የልማት ስራዎች እንዲከወኑ ትልቅ ድርሻ አበርክቷል ያሉት የተቋሙ ስትራቴጂክ አመራሮች እና የፖሊስ መኮንኖች ባለፉት ስድስት ዓመታት በተቋሙ ሲተገበር የቆየው የለውጥ ሂደት ላይ ለመወያየት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በተዘጋጀው የውይይት መርሃ ግብር ላይ ነው፡፡
-
''አፍሪፖልን (AFRIPOL) ማጠናከር የአፍሪካ የፖሊስ ተቋማት በዓለም መድረክ ላይ ያላቸውን ሚና ያሳድጋል።'' ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል( Federal News)
ሩዋንዳ - ኪጋሊ፣ ጥር 21 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ) ክቡር የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል አፍሪፖልን (AFRIPOL) ማጠናከር የአፍሪካ የፖሊስ ተቋማት በዓለም መድረክ ላይ ያላቸውን ሚና ያሳድጋል ያሉት በሩዋንዳ ኪጋሊ እየተካሄደ ባለው 26ኛው የምስራቅ አፍሪካ የፖሊስ አዛዦች ህብረት ድርጅት (EAPCCO) ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ነው።
የሚሰጡ አገልግሎቶች
የሚሰጡ አስተዳደራዊ አገልግሎቶች
- ጥቆማና አቤቱታ መቀበልና የአቅራቢዎችን ቃል መቀበል
- የህዝብ ክንፍ መድረክ በማዘጋጀት የዜጎችን መረጃ የማግኘት መብት ማረጋገጥና የተቋሙን አፈጻጸም እንዲገመግሙ ማድረግ
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጡ አገልግሎቶች
- የማህበረሰብ አገልግሎት (Community Service) ስራዎችን ማከናወን፣
- ስለወንጀል መከላከልና ምርመራ ሀገር አቀፍ ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችንና አንድ ወጥ የሆኑ የአሠራር ደረጃዎችን ማዘጋጀት
በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጤና አገልግሎት የሚሰጡ አገልግሎቶች
- የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት ለሰራዊቱና ለህግ ታራሚዎች መስጠት፤
- የተኝቶ ህክምና አገልግሎት መስጠት
በወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የሚሰጡ አገልግሎቶች
በክስ መቀበል አገልግሎት
- የወንጀል ጥቆማዎችንና አቤቱታዎችን መቀበል፣
- የቀረበው አቤቱታ ጥቆማ ወንጀል መሆን አለመሆኑን እና በፌደራል የማጣራት ስልጣን ስር የሚወድቅ መሆን አለመሆኑን መወሰን፣