አዳዲስ ዜናዎች!
-
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ - የተለወጠ ተቋም ያደገ አሰራር( Federal News)
ኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስን ሪፎርም ማድረግ ያስፈለገባቸው ዋና ዋና ምክንያቶች በዓለማችን ከቴክኖሎጂ እድገትና ከግሎባላይዜሽን ጋር ተያይዞ የወንጀል አድራጊዎች አሰራር እየመጠቀ መምጣቱ እና ድንበር ዘለል ወንጀሎች የሀገራችን ፈተና መሆናቸው ተቋሙን ዳግም ማዋቀር ግድ አድርጎታል።
ከዚህም በተጨማሪ ተቋሙ ዘመኑ ያፈራቸውን ቴክኖሎጂዎች እና የሎጅስቲክስ አቅም ከመጠቀም አንፃር ሰፊ ክፍተቶች የነበሩበት በመሆኑ፣ ከዘመኑ ጋር አብሮ የሚራመድ የፖሊስ ኃይል መገንባት አስፈልጓል።
-
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከባህላዊ አሠራር ወደ ዘመናዊ ስማርት የፀጥታ ተቋም( Federal News)
በመረጃና ቴክኖሎጂ ፈጣን ምጥቀት በሚመራው የዛሬው ዓለም የዲጂታል ሥርዓትን መዘርጋት ለአንድ የፀጥታና የደህንነት ተቋም ከአማራጭነት ይልቅ ህልውናን የማስከበር ያህል ወሳኝ ግዴታ እየሆነ መጥቷል።
ለዛሬዋና ለነገዋ ኢትዮጵያ አስተማማኝ ሰላምና ደህንነት ዘብ የሚቆመው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በዲጂታል ቴክኖሎጂ ታግዘው የሚፈፀሙ ውስብስብ ወንጀሎችን የመከላከልና የመመርመር አቅሙን ለማሳደግ ታላቅ የትራንስፎርሜሽን እርምጃ ላይ ይገኛል።
ተቋሙ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን መነሻ በማድረግ ውስጣዊ አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ሲስተም በማሸጋገር ዘመኑን የሚመጥንና ተወዳዳሪ የሆነ የፖሊስ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።
-
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የፎረንሲክ ምርመራና የምርምር ልህቀት ማዕከል( Federal News)
መንግስት ባለፉት ስምንት ዓመታት በኢትዮጵያ የጸጥታና ደህንነት ተቋማት ሲሰራ የነበረው ሪፎርም የሕግ አስከባሪ አካላት ዘመናዊ እንዲሆኑ በሰው ኃይል፣ በእውቀትና በቴክኖሎጂ እንዲደራጁ ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። ሕዳር 7 ቀን 2017 ዓ.ም በክቡር የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የፎረንሲክ ምርመራና የምርምር ልህቀት ማዕከልም ይህንን ዘመናዊ የለውጥ ጉዞ በተግባር የሚያሳይ ነው።
-
"የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በየዓመቱ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ በመሳተፍ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ችግኞችን በመላው ሀገራችን በተሳተፈባቸው ቦታዎች ሁሉ እየተከለ ይገኛል" የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ ኣዛዥ( Federal News)
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ ኣዛዥ ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በየዓመቱ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ በመሳተፍ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ችግኞችን በመላው ሀገራችን በተሳተፈባቸው ቦታዎች ሁሉ እየተከለ ይገኛል ያሉት በዛሬው ዕለት በጋራ ተስፋን እንትከል በሚል መሪ ቃል በተካሄደው በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ ነው ።
-
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር ክቡር አኒል ኩማር ራይን በቢሯቸው ተቀብለው አነጋገሩ።( Federal News)
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር ክቡር አኒል ኩማር ራይን በቢሯቸው ተቀብለው ያነጋገሩት አምባሳደሩ የቆይታ ጊዜያቸውን አጠናቀው ወደ ሀገራቸው በሚሄዱበት ወቅት ነው።
-
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢንተርፖልና ከማላዊ ፖሊስ ጋር በመተባበር አደገኛ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪ አድነው ባሻው ውዳሞን በቁጥጥር ሥር አዋለ( Federal News)
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢንተርፖል እና ከማላዊ ፖሊስ ጋር በመተባበር በበርካታ የሀገራችን ወጣቶች ላይ ከባድ ኢሰብአዊ ድርጊት ሲፈጽም የቆየውን አደገኛ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪ አድነው ባሻው ውዳሞን በማላዊ ሀገር በቁጥጥር ሥር እንዲውል በማድረግ በሕግ ተጠያቂ እንዲሆን ወደ ሀገራችን እንዲመጣ አድርጓል።
የሚሰጡ አገልግሎቶች
የሚሰጡ አስተዳደራዊ አገልግሎቶች
- ጥቆማና አቤቱታ መቀበልና የአቅራቢዎችን ቃል መቀበል
- የህዝብ ክንፍ መድረክ በማዘጋጀት የዜጎችን መረጃ የማግኘት መብት ማረጋገጥና የተቋሙን አፈጻጸም እንዲገመግሙ ማድረግ
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጡ አገልግሎቶች
- የማህበረሰብ አገልግሎት (Community Service) ስራዎችን ማከናወን፣
- ስለወንጀል መከላከልና ምርመራ ሀገር አቀፍ ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችንና አንድ ወጥ የሆኑ የአሠራር ደረጃዎችን ማዘጋጀት
በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጤና አገልግሎት የሚሰጡ አገልግሎቶች
- የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት ለሰራዊቱና ለህግ ታራሚዎች መስጠት፤
- የተኝቶ ህክምና አገልግሎት መስጠት
በወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የሚሰጡ አገልግሎቶች
በክስ መቀበል አገልግሎት
- የወንጀል ጥቆማዎችንና አቤቱታዎችን መቀበል፣
- የቀረበው አቤቱታ ጥቆማ ወንጀል መሆን አለመሆኑን እና በፌደራል የማጣራት ስልጣን ስር የሚወድቅ መሆን አለመሆኑን መወሰን፣