ኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ETHIOPIAN TECH EXPO 2025 ላይ በሪፎርሙ ያፈራቸውን ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ለሕዝብ እይታ አቀረበ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 09 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ) ኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ “አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ለአፍሪካ ብልጽግና እና ትብብር” በሚል ጭብጥ እና “አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ለአፍሪካ” በሚል መርሃ ግብር የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር እና የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በጋራ ባዘጋጁት ከግንቦት 8 እስከ ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም እየተካሄደ ባለው ETHIOPIAN TECH EXPO 2025 ላይ በሪፎርሙ ያፈራቸውን ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በሲኤምሲ አፍሪካ ኮንቬንሽን ሴንተር ለሕዝብ እይታ አቅርቧል።

498972167_1082726110552438_356574960198550875_n_1747507552.jpg

የኢትዮጵያ ቴክ ኤክስፖ ላይ ተቋሙ የወንጀል መከላከል እና የወንጀል ምርመራ ሥራን ውጤታማ ለማድረግ አገልግሎት ላይ ያዋላቸውን በተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች በዱባይ በተካሄደው የዓለም አቀፍ የፖሊስ ጉባኤ ላይ ምርጥ የፖሊስ መተግበሪያ ሆኖ በአንደኝነት ደረጃ ሽልማት ያሸነፈበትን የዜጎች መተግበሪያ (EFPApp)፣ በCCTV ካሜራ፣ በዲጂታል ፖሊስ ሬድዮ፣ በዲጂታል ፎረንሲክ እና በድሮን ኃይል (Drone force) የገነባውን አቅም የሚያሳዩ ቴክኖሎጂዎችን ለሕዝብ እይታ በማቅረብ በርካታ ሕዝብ እያስጎበኘ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ቴክ ኤክስፖው መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ሳይበር ሴኩሪቲ ልዑካን ቡድን ተገኝተዋል፡፡

የታተመበት ቀን:-2025-05-16
ተጨማሪ ዜናዎች