በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ለአሽባሪና ለፅንፈኛ ቡድኖች ሊደርስ የነበረ ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያ በቁጥጥር ሥር ዋለ
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ግልገል በለስ ከተማ ለአሽባሪና ለፅንፈኛ ቡድኖች ሊደርስ የነበረ ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያ በቁጥጥር ሥር መዋሉን ፖሊስ አስታውቋል።
ፖሊስ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ሚያዝያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በጋራ ባካሄዱት የተቀናጀ ኦፕሬሽን፤ በአንድ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ ተደብቆ የነበረ 163 የብሬን ጥይት እንዲሁም አንድ ፋልኮን ሽጉጥ ከ9 መሰል ጥይቶች ጋር መያዙ ተገልጿል።
በወንጀል ድርጊቱ ላይ ተሳታፊ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ የገለፀው የክልሉ ፖሊስ ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውርን ለመከላከል ከሌሎች የፀጥታ አካላትና ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት በከፍተኛ ትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቋል።
ኅብተረሰቡም መሰል ሕገ-ወጥ ድርጊቶችንና አጠራጣሪ ሁኔታዎችን ሲመለከት ለፖሊስ መረጃ በመስጠት የተለመደ ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ቀርቧል።
የታተመበት ቀን:-2026-04-28